*******************************************************************
ዶ/ር መረራን በእደዚህ አይነት ሁኔታ ማየት ለኦሮሞ ህዝብ ብሔራዊ ውርደት ነው። ይህ የሚያመለክተው የኦሮሞ ህዝብ አንድ ያልተሻገረውና መሻገር ያለበት ትልቅ ድልድይ አለ። እርሱም አንድ የፓለቲካ ማህበረሰብ መሆን ነው።
አንድ ህዝብ የፓላቲካ ማህበረሰብ የሚሆነው ሶስት ዋና ዋና ነገሮችን ስያሟለ ነው።
1ኛ፣ አንደኛውና የአንድ ህዝብ ተቀዳሚ ተግባሩ ልጆች ወልዶ ማሳድግና መሪዎቹን ከውጭ ጥቃት መከላከል መቻል ነው። ልጆቹንና መሪዎቹን ከውጭ ጥቃት መከላከል ብቻ ሳይሆን ጥቃት ለማድረስ የሚያስብ አካል ከለ ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍል ወይም ጦርነት የሚያስነሳ መሆኑን ተገንዝቦ ዋጋውን ቁጭ ብሎ እንዲተምን የሚያስገድድ የተፈራና የተከበረ ህዝብ ሲሆን ነው። በርካታ የአለም ትላልቅ ጦርነቶች የተነሱት ህዝቦች ራሳቸውን ከዚህ መሰል ጥጋበኞች ለመከላከል ሲሉ ነው።
ሌሎች ልጆቹን እና መሪዎችን በዘፈቀደ በሚገሉበት፣ በሚያስሩበት፣ ከሰፈለጋቸውም የራሳቸው ባሪያ ልያደርጉ በሚችሉበት ሁኔታ የፓለቲካ መህበረሰብ መሆን ብሎ ነገር የለም፣ እንደዚህ አይነት ህዝብ ለራሱ አስከብራለው ብሎ የሚያወራው ሌላ መብት የለውም። ካለን አይደለ ስለሌላ የምንናገረው?
2ኛ፣ አንድ ህዝብ የፓላቲካ ማህበረሰብ ሆነ የሚበለው የራሱን መሬትና የግዛት አንድነት ማስከበርና መጠበቅ ስቺል ነው። መሬት ያሌላው ህዝብ አገር የለውም።
3ኛ፣ አንድ ህዝብ የፓላቲካ ማህበረሰብ ሆነ የሚባለው የጋራ ሃብቱና የማንነት መገለጫ የሆኑትን ቋንቋውን እና ባህሉን ጠብቆ በዚያ ቋንቋና ባህል መኖርና ራሱን ማስተዳዳር ሲቺል ነው። ኣሳ ከውሃ ውጭ መኖር እንደማይችል ሁሉ አንድ ህዝብ ቋንቋውንና ባህሉን ጠብቆ በዚያ ውስጥ ከልኖረ የሞተ ህዝብ ነው። የኦሮምኛ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ መሆን ከዚህ ውጭ ሌላ ትርጉም የለውም።
የዚህ ትውልድ የኦሮሞ ህዝብና የኦሮሞ ወጣቶች ግንበር ቀደም አላማና ተልእኮም የኦሮሞ ህዝብን ወደ አንድ የፓለቲካ ማህበረሰብ ማሻጋገርና የኦሮሞ ህዝብን በቀዬው በኦሮሚያና በከተማው በአዲስ አበባ ላይ አባ ወራ፣ በአገሩ በኢትዮጵያ ላይ በለአገርና ባለቤት ማድረግ ነው።
እዚህ ላይ ሁሉም መገንዘብ ያለበትና ፉፁም ልስተው የማይገባ እውነታ በእነዚህ ሶስት ዋና ዋና ብሄራዊ ጉዳዮች ላይ በኦሮሞ ህዝብ መካከል የፓለቲካ፣ የሃይማኖት ወይም የአከባቢ ልዩነት ያሌለ መሆኑን ነው።
የኦሮሚኛ ቋንቋ ሃይማኖት፣ ወይም ክልል፣ ወይም የፓላቲካ አስተሳሰብ የለውም። የኦሮሞ ህዝብ የጋራ ሃብት ነው።
የኦሮሞ ህዝብ መሬት ሃይማኖት፣ ወይም ክልል፣ ወይም የፓላቲካ አስተሳሰብ የለውም። የኦሮሞ ህዝብ ሁሉ የጋራ መኖርያውና በጋራ የሚጠብቀው የጋራ ሃብት ነው።
ለነዚህ ሶስት አላማዎች በመቆማቸው የሚፈሰው የኦሮሞ ልጆች ደምና የሚወረዱት የኦሮሞ መሪዎች ሃይማኖት፣ ወይም ክልል፣ ወይም የፓላቲካ አስተሳሰብ የላቸውም። ህዝባችን በጋራ ልጠብቃቸውና ዘብ ሊቆምላቸው የሚገቡ የኦሮሞ ህዝብ ልጆችና መሪዎች ናቸው።
ስለዚህ የኦሮሞ ህዝብ: ህዝብ ሆኖ ለመቀጠል፣ የሞቱትን ልጆቹንና መሪዎቹን አልቅሶ ከመቅበር አልፎ በሃይማኖት፣ በፓለቲካ አስተሳሰብ፣ እና በአከባቢ ሳይለያይ አንድ የፓለቲካ ማህበረሰብ ሆኖ በህይወት ላሉት ልጆቹና መሪዎቹ ደህንነትና ክብር መቆም አለበት።
የኦሮሞ ወጣቶችም ግንባር ቀደም ሥራና ምናልባትም ብቸኛው ኃላፊነት ይኸው መሆን አለበት። ምክንያቱም እነዚህ ሶስቱ ዋና ዋና የህዝባችን የህልውና ምሰሶዎች (በተቀመጡበት ቅደም ተከተል) ካሌሉ ሌላው ሁሉ የለም።
November 10, 2023 Fatansaa Sulee Shogodoo The interest of this article is not to do…
Amhara Fano continued to attack Oromo civilians. In this latest incident, at least 17 people…
Deebitee Kootee Bilisoo October 25, 2023 Note that a political slogan stands for a cause.…
October 17, 2023 Mallisee Fatansaa Sulee Recently, a chorus of diaspora Amhara social media, the…
September 26, 2023 Deebitee Kootee Billisoo During the Abyssinian War of the conquest of Oromia,…
Fatansaa Sulee Shogodoo September 20, 2023 As it is clear from hateful and Oromo phobia…